Sidama Hawassa
+251-462-12-6495
dagoomuf@sidaamaphi.org

በሲዳማ ክልል የህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት አዘጋጅነት እየተካሄደ የሚገኘው 10ኛው የድንገተኛ አደጋዎች ቅኝትና ምላሽ ፎረም ተሳታፊዎች ከውይይቱ ጎን ለጎን በክልሉ ውስጥ የተሰሩ ለተሞክሮ የሚሆኑ ሥራዎችን ጎብኝተዋል።

ከተጎበኙት ተቋማት መካከል በሀዋሳ ከተማ የሚገኘው የሚሊኒየም ጤ/አ/ጣቢያ የጤናና ጤና ነክ ድንገተኛ አደጋዎች ቅኝትና ምላሽ ሥራ እየተመራ ያለበትን አሠራር ፣ በኢንስቲትዩቱ የድጂታል ላይብራሪ እና በመስሪያ ቤቱ ህንጻ ላይ እየተተገበረ የሚገኘው የጽዱ ኢትዮጵያ ፕሮጀክት ይገኙበታል።

ከ20 በላይ የሚሆኑ የህዝብ ተወካዮች ም/ቤት አባላትን እና ሌሎች ከየክልል ቢሮዎች እንዲሁም ከፌደራል መ/ቤቶች የተወጣጡ ተሳታፊዎችን ያካተተው ጉብኝት ላይ የነበሩ እንግዶች በክልሉ ጤና ኢንስቲትዩት ለተሞክሮ የሚሆኑ ሥራዎች መሠራታቸውን በሰጡት አስተያየት ከመግለጻቸውም በላይ ዕድሉን አግንተው ይህን ምርጥ ሥራ መጎብኘታቸው እንዳስደሰታቸው ተናግረዋል ።

 የማይበገር የህብረተሰብ ጤና አደጋ ቁጥጥር ስርዓት    ለብሄራዊ ጤና ደህንነት  !

የሲዳማ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲዩት
የካቲት 1/2017 ዓ.ም
ሐዋሳ

ተጨማሪ መረጃዎችን የሲዳማ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት
ነፃ የስልክ መስመር፡ 7794
Web site: https://www.sphi.gov.et/

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *