Sidama Hawassa
+251-462-12-6495
dagoomuf@sidaamaphi.org

Author: admin

የሲዳማ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የ2017 በጀት ዓመት የ4 ወራት የዕቅድ አፈፃፀም ግምገማ መድረክ በዛሬው ዕለት የተለያዩ ባለድርሻ አካላትና የወባ ማሕበራት በተገኙበት አካሄደ፡፡

የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ዳመኔ ደባልቄ በመድረኩ መልዕክት ባስተላለፉበት ወቅት የህብረተሰብ ጤና አደጋዎችን ለመከላከልና ለመቆጣጠር ዘርፈ-ብዙ ተግባራት እንደተተገበሩ ገልፀው የወባ ጫናን ለመቀነስና ለመከላከል ከአካባቢ ቁጥጥር ስራ ባለፈ ሕብረተሰቡ የፀረ-ወባ ትንኝ ኬሚካል ርጭትንና የአልጋ አጎበርን በአግባቡ መጠቀም እንዳለበት ገልፀዋል። በመቀጠልም የሪፖርት ሙሉዕነትንና ወቅታዊነት በመጠበቅ ፣ የግምገማ እና ግብረ መልስ ስርዓትን በመዘርጋት እና ተቋማዊ አንድነትን ማጠናከርን ባህል…
Read more

የጤና ሚኒስቴር አመራሮችና ባለሙያዎች ባለፉት አራት ቀናት በሲዳማ ክልል ሲያደርጉት የነበረውን የተቀናጀ ድጋፋዊ ክትትል አጠናቀው ግብረ መልስ ሰጡ !

የጤና ሚኒስቴር የተቀናጀ ድጋፋዊ ክትትል (ISS) ቡድኑ በሁለት ቡድኖች ተከፋፍለው ባለፉት አራት ቀናት ተዘዋውረው የሥራ እንቅስቃሴያቸውን ከተከመለከቷቸው ጤና ተቋማትና መዋቅሮች መካከል :- የክልሉ ድንገተኛ ክስተቶች መከታተያ ስርዓት (EOC )የክልሉ ጠቅላላ ላቦራቶሪ ፣ ሁለት (2 ) ዞኖችና ሀዋሳ ከተማ (1) ፣ አራት (4) ሆስፒታሎች ፣ አምስት (5) ወረዳዎች ፣ ስምንት ( ጤና ጣቢያዎች ፣ ሰባት (7)…
Read more

የተቀናጀ ድጋፍዊ ክትትል ቡድን በሲዳማ ክልል የጤና ተቋማትን የስራ እንቅስቃሴና የወባ በሽታ የመከላከል ስራ ላይ የማህበረሰቡን ተሳትፎ በመዘዋወር ምልከታ አድርጓል

__________ በጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ወ/ሮ ፍሬህይወት አበበ የተመራው የተቀናጀ ድጋፋዊ ክትትል ቡድን የጤና ተቋማትን የስራ እንቅስቃሴና የወባ በሽታ መከላከል ላይ እየተሰራ ያለዉን የማህበረሰቡን ተሳትፎ ቃኝተዋል። በድጋፋዊ ምልከታቸውም የክልሉ ጠቅላላ ላቦራቶሪ ፣ የሰሜናዊ ሲዳማ ዞን ጤና ዳይሬክቶሬት ፣ አዳሬ እና ይርጋዓለም ጠ/ሆስፒታሎች፣ ወንዶ ገነት የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል፣ የወንዶገነት ወረዳ ጤና ጽ/ቤት፣ ወሻ ጤና ጣቢያን እና…
Read more

በጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ በክብርት ወ/ሮ ፍሬህይወት አበበ የሚመራ የተቀናጀ ድጋፍዊ ክትትል ቡድን በሲዳማ ክልል ስራውን ጀመረ !

የሲዳማ ክልል ጤና ቢሮ ፤ ሕዳር 22/2017ዓ.ም በጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ በክብርት ወ/ሮ ፍሬህይወት አበበ የሚመራ የተቀናጀ ድጋፍዊ ክትትል ቡድን ከቢሮው ማኔጅመንት እና ከተጠሪ ተቋማት ኃላፊዎች አባላት ጋር ውይይት አድርገዋል። የተቀናጀ ድጋፍዊ ክትትል የሚያደርገው የጤና ሚኒስቴር ቡድን በሲዳማ ክልል ሥር የሚገኙ በአራት ዞኖች ፣ ስምንት ወረዳዎች ፣ አራት ሆስፒታሎችን ፣ ስምንት ጤና ጣቢያዎችን እና ስምንት…
Read more

በሲዳማ ሕብረተስብ ጤና ኢንስቲትዩት የፀረ ሙስናና ስነ-ምግባር ቀን በቢሮ ደረጃ ተከበረ ።

ህዳር 23/2017 ዓ.ም ሲዳማ ሕብረተስብ ጤና ኢንስቲትዩት ሀዋሳ በሲዳማ ሕብረተስብ ጤና ኢንስቲትዩት ”ወጣቶችን ያማከለ የፀረ ሙስና ትግል” በሚል መሪ ቃል በሀገራችን ለ20ኛ ጊዜ በክልል ደረጃ ለ19ኛ ዙር በተቋሙ ደረጃ የፀረ ሙስና ቀን ተከበረ ። በውይይት መድረክ ላይ የተቋሙ አጠቃላይ ሰራተኞች እና የማናጅመንት አባላት ተገኝተው ተሳታፍ ሆነዋል :: የሲዳማ ሕብረተስብ ጤና ኢንስቲትዩት ህዳር 23/2017 ዓ.ም ሀዋሳ

የሲዳማ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ”Regional Information Platform for Nutrition (RIPN)” ፕሮጀክት ያከናወናቸውን እና በቀጣይ በሚከናወኑ ተግባራት ዙሪያ ህዳር 18/2017 ዓ.ም ውይይት አካሄደ፤

በመድረኩ የሲዳማ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ምትክል ዋና ዳይሬክተር አቶ ኡጋሞ ሀናጋ እንደተናገሩት ኢንስቲትዩቱ ከተቋቋመበት ዓላማዎች መካከል አንዱ በምርምር ላይ የተመሰረተ የጤና መረጃ በማመንጨት ውሳኔ ሰጪ አካላት እንዲጠቀሙበት ማድረግ እና የምግብና ስርዓተ – ምግብ ስራዎች ውጤታማ እንዲሆኑ እና በእነዚህ ጉዳዮች ላይ ማስተባበር መሆኑን ገልፀው በሚጠበቀው ልክ እየተሰራ ባለመሆኑ በክልሉ ከጉዳዩ ጋር የተያያዙ ዘርፈ ብዙ ችግርን በሚገባ…
Read more

በክልላችን ከፍ እያለ የመጣውን የወባ ወረርሽኝ ለማስቆም ዘርፈ ብዙ ስራ እየተሰራ ይገኛል፤ ከእነዚህም ስራዎች አንዱ የሆነው የምርመራውን አቅምና ጥራት ማሻሻል ነው የሲዳማ ሕብረተስብ ጤና ኢንስቲትዩት ም/ዋና ዳይሬክተር አቶ ኡጋሞ ሀናጋ።

የሲዳማ ሕብረተስብ ጤና ኢንስቲትዩት ከክልል ጤና ቢሮ እና ከይርጋለም ህክምና ኮሌጅ ጋር በመተባበር ”መሠረታዊ የወባ ምርመራ በማይክሮስፒ” በሚል ሪዕስ ከህዳር 9-13/2017ዓ/ም ለላቦራቶሪ ሰራተኞች ስሰጥ የነበረው ስልጠና ተጠናቀቀ። በማጠቃለያው ላይ የተገኙት የኢንስቲትዩቱ ም/ ዋና ዳይሬክተር አቶ ኡጋሞ ሀናጋ በክልላችን ያለውን የወባ ወረርሽኝ ለመግታት የላቦራቶሪ ባለሙያዎች ሚና ትልቅ መሆኑን ገልጸው የነበሩትን ክፍተቶች ለመሙላት ታስቦ የተዘጋጀ እንደሆነም በመግለጽ…
Read more

የዓለም የፀረ ተህዋስያን መድሐኒት በጀርሞች የመላመድ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሳምንት በሐዋሳ ተከበረ

የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ከሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ እና ሌሎች አጋር አካላት ጋር በመተባበር “እናስተምር፣ እናሳውቅ፣ አሁን እንተግብር” በሚል መሪ ቃል የሚከበረውን የዘንድሮውን የዓለም ፀረ ተህዋስያን መድሐኒቶች በጀርሞች መላመድ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሳምንት ከህዳር 12-14/2017 ዓ.ም በሐዋሳ ከተማ አካሄደ፡፡ የኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር መሳይ ኃይሉ በፕሮግራሙ መክፈቻ ላይ እንደገለፁት የዓለም ፀረ ተህዋስያን የመቋቋም ግንዛቤ ማስጨበጫ ሳምንት በዓለም አቀፍ…
Read more