የአንድ ጀምበር የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ-ግብር በሀዋሳ ከተማ በሀዌላ ቱላ ክ/ከተማ ጫሬ በተሰኘ ሰፍራ ተካሄደ
*****
“በመትከል ማንሰራራት”
የሲዳማ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት
ሀምሌ 24/2017 ዓ/ም
ሀዋሳ
ተጨማሪ መረጃዎች የሲዳማ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት
ነፃ የስልክ መስመር፡ 7794
Web site: https://sphi.gov.et



















Get the latest public health alerts and emergency updates from Sidama Public Health Institute.





















የሲዳማ ክልል ሁሉም ኢትዮጵያውያን በክብርና በአንድነት የሚኖሩበት የህብራዊነት መገለጫ ነው ሲሉ የሲዳማ ክልል ም/ርዕሰ መስተዳድርና የት/ት ቢሮ ኃላፊ አቶ በየነ ባራሳ ገለጹ። በሲዳማ ክልል የጳጉሜ 2 የህብር ቀን ”ብዝኃነት የኢትዮጵያ ጌጥ” በሚል መሪ ቃል በተለያዩ መርሐግብሮች ተከብሯል። ዕለቱን አስመልክቶ መልዕክት ያስተላለፉት አቶ በየነ ባራሳ አንደገለጹት እናት ሀገራችን ኢትዮጵያ በብዝሀ ማንነቶች የጠነከረች የሁላችንም ቤት ናት ብለዋል፤…

************ ፖሊዮ/የልጅነት ልምሻ በፖሊዮ ቫይረስ አማካይነት የሚመጣ ተላላፊ በሽታ ሲሆን በአብዛኛው ልጆችን የሚያጠቃ በሽታ ነዉ፡፡ ቫይረሱ ለዕድሜ ልክ አካል ጉዳተኝነት የሚያጋልጥ እና አልፎ ተርፎም በሰዓታት ውስጥ ለሞት ሊዳርግ የሚችል ነዉ። የፖሊዮ ኢንፌክሽን ዓይነቶች ምንም ዓይነት ምልክት የማያሳይ (Asymptomatic) በፖሊዮ ቫይረስ ከተያዙ ሰዎች 90-95% የሚሆኑት ምንም ዓይነት የሚታይ ምልክት አያሳዩም። ነገር ግን ቫይረሱን ማሰራጨት እና ሌሎችን…

ስለ ጤናዎ ምንም አይነት ጥያቄ ወይንም ስጋት ካለዎት በ7794 ነፃ የስልክ መስመር ደዉለው ሙሉ መረጃ ማግኘት ይችላሉ :: ኮሌራ ፣ወባ ፣ኩፉኝ —–ወ ዘ ተ ማንኛዉም ጤና እና ጤና ነክ መረጃ እና ምክር አግልግሎቶችን ብቃት ባላቸው የጤና ባለሙያዎች በሳምንት 7ቀን ለ 24ሰዓታት አግልግሎት እየሰጡ ይገኛሉ ::

የሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ጤና ቢሮ፣ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩትና ሌሎች ባለድርሻ አካላት በተገኙበት በክልሉ አንዳንድ አከባቢ የተከሰቱ የኮሌራ ወረርሽኝ እና የወባ በሽታ ስርጭት ያለበት ደረጃ ተገምግሟል፡፡ መድረኩን በይፋ ያስጀመሩት የክልሉ ጤና ቢሮ ኃላፊዋ ዶ/ር ሰላማዊት መንገሻ ሲሆኑ ከክረምት ጋር ተያይዞ አንዳንድ ወረዳዎች የተከሰቱ የኮሌራ ወረርሽኝ እና የወባ በሽታ ስርጭት ከሚጠበቀዉ በላይ መሆኑ አሳሳቢ የህብረተሰብ ጤና…

የኢትዮጵያ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር መሳይ ሀይሉ በሀዋሳ ከተማ ለ100 ሁለገብ ባለሙያዎች የአንድ ወር ስልጠና ከፈቱ። ስልጠናው በ24 – 48 ሰአታት ውስጥ በድንገተኛ አደጋዎች ለመሰማራት ዝግጁ የሆኑ በደንብ የሰለጠኑ፣ የታጠቁ፣ ቀልጣፋ እና ተለዋዋጭ ባለሙያዎችን ዝርዝር በማዘጋጀት ለጤና ድንገተኛ አደጋዎች ምላሽ ለመስጠት ምላሽ ሰጪ ቡድኖችን ማጠናከር እና መጠቀም ላይ ያተኩራል። ስልጠናው የኢፒአይአይ ከጤና ጥበቃ…

ኢንስቲትዩቱ የዘመቻ ክትባቱን አስመልክቶ ከባለድርሻ አካላት ጋር የንቅናቄ መድረክ እያደረገ ይገኛል፡ የሲዳማ ክልል የህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ዳመነ ደባልቄ በመልዕክታቸው ፥ የፖሊዮ በሽታን እንደ ሀገር ለማጥፋት ከ1972 ዓ.ም ጀምሮ በርካታ ስራዎች ቢሰሩም አሁንም በሽታው አለመጥፋቱን ገልፀዋል ። ዋና ዳይሬክተሩ አክለውም እንደ ሲዳማ ክልል የተከሰተ የፖሊዮ በሽታ ባይኖርም እንደሀገር በሰባት ክልሎችና አዲስ አበባ ከተማ…