Sidama Hawassa
+251-462-12-6495
dagoomuf@sidaamaphi.org

የሲዳማ ብ/ክ/መንግስት ጤና ቢሮ እና ተጠሪ ተቋማት የብልጽግና ፓርቲ መሰረታዊ ድርጅት የአባላት ኮንፈረንስ ማካሄድ ተጀመረ ።

በጤና ቢሮ እና በተጠሪ ተቋማት እያገለገሉ የሚገኙ የብልጽግና ፓርቲ  መሠረታዊ ድርጅት  ሥር የሚገኙ አመራር እና ሰራተኞች በፓርቲው  የዘጠኝ ወር የስራ አፈጻጸም ሪፖርት ላይ ውይይት እየተካሄደ ይገኛል።

 በተያያዘም በዚሁ ሪፖርት ተለይተው የወጡ ጉድለቶችን ለመሙላት ዛሬ የተደረገው ውይይት ለፓርቲው አባላት  የበለጠ አቅም እንደሚፈጥርና ሁሉም አመራርና አባላት ተቀራራቢ የሆነ አቋም እንዲኖራቸው ያስችላል ተብሎም ይጠበቃል።

በኮንፈረንሱ  በስራቸው የተሻለ ዉጤት ላስመዘገቡ የድርጅቱ አባላት ማበረታቻ የሚሰጣቸው ሲሆን ይህም አባላትን ለበለጠ ተልዕኮ እንዲዘጋጁ   እና በቀጣይ የአገር እና የቤተሰብ ብልፅግናን ለማረጋገጥ ጠቄሜታ እንዳለውም  በመድረኩ ተገልጿል።

የሲዳማ ሒብረተሰብ ጤና ኢንሰቲትዩት

ሚያዚያ 23/2015 ዓ.ም

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *