አሳዛኝ ዜና
እህታችን ስምረት ባደረባት ህመም በህክምና ስትረዳ ቆይታ ትናንት ምሽት አርፋለች ። ስለሆነም የአስከሬን አቀባበል ለማድረግ ዛሬ 8:00 ላይ ጥቁር ዉሀ እንገናኝ ።
ፈጣሪ ለቤተሰብ እንድሁም ወዳጅ ዘመድ መፅናናትን ይስጥ።




Get the latest public health alerts and emergency updates from Sidama Public Health Institute.






በኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ዓለም አቀፍ የጤና ደንብ እና የአንድ ጤና ፅ/ቤት፣ ከሲዳማ ክልል የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት፣ አለም አቀፍ የጤና ድርጅት እና ከተለያዩ አጋር አካላት ጋር በመተባበር የሲዳማ ክልል የጤና ደህንነት አቅም ለማጠናከር የሚያስችል የግምገማ አውደ ጥናት ከሰኔ 4 እስከ 6 /2017 ዓ.ም በአዳማ ከተማ እያካሄደ ነው:: የሕብረተሰብ ጤና አደጋ መከላከልና ዝግጁነት ስራዎችን በሚገባ ተግባራዊ…

የሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ጤና ቢሮ ሃላፊ ዶ/ር ሰላማዊት መንገሻ ምርጥ የጤና ዘርፍ አመራር ሽልማት የተሸለሙ ሲሆን ሽልማቱን የሰጠው የማህበረሰብ ጤና አገልግሎት ሀገር በቀል ማህበር ነው። የሲዳማ ሕብረተስብ ጤና እንስቲትዩት ዶ/ር ሰላማዊት መንገሻ ላበረከቱት በሳል አመራር እያመሰገነ የማህበረሰብ ጤና አገልግሎት ላበረከተሎት ሽልማት እንኳን ደስ አለዎት ለማለት ይወዳል። የሲዳማ ሕብረተስብ ጤና እንስቲትዩት ሚያዚያ 07/2016 ዓ.ም ሀዋሳ,ሲዳማ

ከተጎበኙት ተቋማት መካከል በሀዋሳ ከተማ የሚገኘው የሚሊኒየም ጤ/አ/ጣቢያ የጤናና ጤና ነክ ድንገተኛ አደጋዎች ቅኝትና ምላሽ ሥራ እየተመራ ያለበትን አሠራር ፣ በኢንስቲትዩቱ የድጂታል ላይብራሪ እና በመስሪያ ቤቱ ህንጻ ላይ እየተተገበረ የሚገኘው የጽዱ ኢትዮጵያ ፕሮጀክት ይገኙበታል። ከ20 በላይ የሚሆኑ የህዝብ ተወካዮች ም/ቤት አባላትን እና ሌሎች ከየክልል ቢሮዎች እንዲሁም ከፌደራል መ/ቤቶች የተወጣጡ ተሳታፊዎችን ያካተተው ጉብኝት ላይ የነበሩ እንግዶች…

የሲዳማ ክልል ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ሐምሌ 1/2018 ዓ.ም የሲዳማ ክልል ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ለሐዋሳ ደም ባንክ ሠራተኞች በመልካም የማምረት አተገባበር (Good Manufacturing Practice–GMP) ላይ ስልጠና ሰጥቷል። የስልጠናውን መርሃ ግብር ያስጀመሩት የሲዳማ ክልል ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ምክትል ዳይሬክተር አቶ ኡጋሞ ሀናጋ በንግግራቸው ፣ እንዲህ ያሉ የአቅም ግንባታ ስልጠናዎች የደም ባንኩን የአገልግሎት ጥራትና ደህንነትን ለማሻሻል ከፍተኛ ሚና…

የሲዳማ ብ/ ክ/መንግስት ጤና ቢሮ በሀገር አቀፍ ደረጃ የቲቢ በሽታን ለመግታት በተደረገው እንቅስቃሴ ከፍተኛ ውጤት በማስመዝገብ የዋንጫና የሰርተፊኬት ተሸላሚ ሆኗል:: ለዚህ ውጤት መገኘት የበኩላችሁን የተወጣችሁ የጤና ቢሮ ማኔጅመነትና ሠራተኞች እንዲሁም በተለያዩ መዋቅሮች የምትገኙ የጤናው ሴክተር አመራሮችና ባለሙያዎች እንኳን ደስ አለን /አላችሁ !! ሲዳማ ሕብረተስብ ጤና እንስቲትዩት መጋብት 13/2016 ዓ፡ም ሀዋሳ/ሲዳማ

Proper Testing During a Marburg Epidemic