

















Get the latest public health alerts and emergency updates from Sidama Public Health Institute.


የሲዳማ ክልል ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ሚያዚያ 06/2018 ዓ.ም በኮንፈረንሱ መድረክ ላይ የተገኙት የሲዳማ ክልል ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ዳመነ ደባልቄ ባስተላለፉት መልዕክት ጠንካራ ሀገር ለመገንባትና የተጀመረውን ፈጣን ልማት ለማስቀጠልና ለማሳለጥ በሚደረገው ሁለንተናዊ ጥረት የአባላት ሚና የጎላ መሆኑን ገልፀዋል። እንደ ክልል ኢንስቲትዩቱ የህዝቡን ጤና አደጋ ላይ የሚጥሉ የሕብረተሰብ ጤና ስጋቶችን ለመከላከልና ለመቆጣጠር እየሰራ እንደሚገኝ…

የሲዳማ ክልል ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ሐምሌ 23/2018 ዓ.ም የሲዳማ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የላቦራቶሪ ዳይሬክቶሬት የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ፣ የተሻለ ውጤት ላስመዘገቡ የጤና ተቋማት የዕውቅናና የ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ ትውውቅ መድረክ አካሂዷል። በመድረኩ የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር ክቡር ዶ/ር ዳመነ ዳባልቄ እንደገለጹት፣ 2018 በጀት ዓመት ለኢንስቲትዩቱ ከፍተኛ ስኬቶች የተመዘገቡበት ዓመት ሲሆን፣ ይህም ውጤት በየደረጃው ያሉ…

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 20፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የኤም ፖክስ (Mpox) በሽታ እንዳይዛመት በትኩረት እየተሰራ ነው አሉ የጤና ሚኒስትር ዶክተር መቅደስ ዳባ፡፡ ሚኒስትሯ ጉዳዩን አስመልክተው በሰጡት መግለጫ እንዳሉት÷በኦሮሚያ ክልል ሞያሌ ከተማ አስተዳደር በኤም ፖክስ ከተጠረጠሩ ሰዎች በተወሰደ ናሙና እስካሁን የአንድ ቤተሰብ አባላት የሆኑ ሶስት ሰዎች ላይ በሽታው ተገኝቷል፡፡ በሽታውን ለመከላከልና ለመቆጣጠር የተጠናከረ ጥረት እየተደረገ መሆኑን…

ከተጎበኙት ተቋማት መካከል በሀዋሳ ከተማ የሚገኘው የሚሊኒየም ጤ/አ/ጣቢያ የጤናና ጤና ነክ ድንገተኛ አደጋዎች ቅኝትና ምላሽ ሥራ እየተመራ ያለበትን አሠራር ፣ በኢንስቲትዩቱ የድጂታል ላይብራሪ እና በመስሪያ ቤቱ ህንጻ ላይ እየተተገበረ የሚገኘው የጽዱ ኢትዮጵያ ፕሮጀክት ይገኙበታል። ከ20 በላይ የሚሆኑ የህዝብ ተወካዮች ም/ቤት አባላትን እና ሌሎች ከየክልል ቢሮዎች እንዲሁም ከፌደራል መ/ቤቶች የተወጣጡ ተሳታፊዎችን ያካተተው ጉብኝት ላይ የነበሩ እንግዶች…
በመረጃ ላይ የተመሰረተ ውሳኔ አሰጣጥ (Evidence-Informed Decision-Making – EIDM) ጉባኤ በአድዋ ሙዚየም አዳራሽ እየተካሄደ ሲሆን የጤና ስርዓቶችን በዕውቀት፣ በማስረጃና በትብብር ማጠናከር የወቅቱ ቁልፍ አጀንዳ መሆኑ ተገለጸ። በጉባኤው መክፈቻ ንግግር ያደረጉት የኢትዮጵያ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ዶክተር መሳይ ኃይሉ፣ ጉባኤው የጤና ስርዓቶችን በዕውቀት፣ በማስረጃና በትብብር ለማጠናከር ያለውን የጋራ ቁርጠኝነት የሚያንፀባርቅ መድረክ መሆኑን ገልጸዋል። ዶክተር መሳይ…

(ምንጭ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ ) ሚንስቴር መስሪያ ቤቱ ለጅንካ ሆስፒታል የማርበርግ ቫይረስን ለማከምና ለሌሎች ህክምናዎች የሚያስፈልጉ የተለያዩ የህክምና ቁሳቁሶችን ድጋፍ አድርጓል። ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ እና የኢፌድሪ ጤና ሚኒስቴር ሚንስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ በጅንካ ሆስፒታል በመገኘት የማርበርግ ቫይረስን ለመከላከል እና ስርጭቱን ለመቆጣጠር በመከናወን ላይ የሚገኙ የክትትል ስራዎች ምልከታ አድርገዋል። ርዕሰ መስተዳድሩ በምልከታው ወቅት…