አዲሱን የጤና አገልግሎት አስተዳደር እና ቁጥጥር አዋጅ ቁጥር 1362 2017 በተመለከተ የተደረገ የባለሙያዎች ፓናል ውይይት – ክፍል አንድ እና ሁለት:-
ክፍል አንድ
ክፍል ሁለት
Get the latest public health alerts and emergency updates from Sidama Public Health Institute.
ክፍል አንድ
ክፍል ሁለት

የኢትዮጵያ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር መሳይ ሀይሉ በሀዋሳ ከተማ ለ100 ሁለገብ ባለሙያዎች የአንድ ወር ስልጠና ከፈቱ። ስልጠናው በ24 – 48 ሰአታት ውስጥ በድንገተኛ አደጋዎች ለመሰማራት ዝግጁ የሆኑ በደንብ የሰለጠኑ፣ የታጠቁ፣ ቀልጣፋ እና ተለዋዋጭ ባለሙያዎችን ዝርዝር በማዘጋጀት ለጤና ድንገተኛ አደጋዎች ምላሽ ለመስጠት ምላሽ ሰጪ ቡድኖችን ማጠናከር እና መጠቀም ላይ ያተኩራል። ስልጠናው የኢፒአይአይ ከጤና ጥበቃ…


የሲዳማ ሕብረተስብ ጤና ኢንስቲትዩት በ2016 በጀት ዓመት የታቀዱ ዋና ዋና ተግባራት ዕቅድ አፈጻጸም ግምገማና የ2017 በጀት ዓመት ዕቅድ ውይይት እየተደረገ ይገኛል። መድረኩን በንግግር የከፈቱት የሲዳማ ክልል ጤና ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር ሰላማዊት መንገሻ ሲሆኑ በንግግራቸውም የኅብረተሰብ ጤና ድንገተኛ አደጋዎችን በመከላከልና በመቆጣጠር ረገድ የተሰሩ በርካታና ዘርፈ-ብዙ ሥራዎች ከክልሉም አልፎ በሀገር-ዐቀፍ ደረጃ ለምርጥ ተሞክሮ የሚሆኑ መሆኑን ገልጸዋል ።…

በዕለቱ እንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር ያደረጉት የኢንስቲትዩቱ ምትክል ዋና ዳይሬክተር አቶ ኡጋሞ ሀናጋ ስሆን ኢንስቲትዩቱ ከተቋቋመባቸው ዓላማዎች መካከል በክልሉ ያለውን የጤና መረጃ በዘመናዊ መንገድ በመሰብሰብና በመተንተን ለውሳኔ ሰጪ አካላት ጥቅም ላይ እንዲውል ማድረግ መሆኑን ገልፀው ክልላዊ ጤና እና ጤና ነክ መረጃ ቅመራ፣ ትንተና እና አስተዳደር ማዕከል [Regional Data Management Center for Health(RDMS)] ተቋቁሞ ከዩኒቨርሲቲዎች፣ ከሴክተር…

__________ በኢትዮጵያ ጤና ሚኒስቴር እና በሩሲያ የሸማቾች መብት ጥበቃ እና የሰብአዊ ደህንነት ክትትል አገልግሎት የመግባቢያ ስምምነቱ ተፈርሟል። ፊርማው የተካሄደው ለመጀመሪያ ጊዜ የሩሲያ-አፍሪካ ለድንገተኛ የጤና አደጋዎች ፈጣን ምላሽ ሰጪ ቡድኖች ልምምድ እና አውደ-ጥናት መርሃ-ግብር ጎንዮሽ ሲሆን፤ በጤና ድንገተኛ አደጋዎች ላይ በሁለቱ አገሮች መካከል ያለውን ትብብር ለማጠናከር ያለመ ስምምነት ነው፡፡ የጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ ኢትዮጵያን ወክለው፣…

በኢንስቲትዩቱ የባክቴሪያል፣ የፓራሳይቲክ እና እንሰሳት ነክ በሽታዎች ምርምር ዳይሬክቶሬት አዘጋጅነት ዶ/ር ደረጄ ዱጉማ የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ድኤታ እና ዶ/ር መሳይ ኃይሉ የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር እንዲሁም ም/ዋና ዳይሬክተሮች በተገኙበት ዓመታዊ የጸረ-ተህዋስያን መድሃኒቶች ብግርነት Ani-microbial Resistance (AMR) የዳሰሳ ጥናት የምክክር መድረክ የካቲት 18 እና 19/2016 ዓ.ም በአዲስ አበባ ከተማ በመካሄድ ላይ ነው፡፡ የምክክር መድረኩ ዋና ዓለማ ኢ.ኤ.አ…