በ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ በቀጣይ በሚተገበሩ ሀገራዊና ክልላዊ ዕቅድ፣ በፓርቲው ማንፌስቶ እንዲሁም በምርጫ መመሪያ ላይ የኢንስቲትዩቱ የብልጽግና ፓርቲ አባላት ዉይይት አደረጉ።

ሀዋሳ፤ሚያዚያ 30/2018 ዓ.ም የሲዳማ ሕብረተሰብ ጤና ኢንሰቲትዩት የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት

”ኢትዮጽያ ወደ ተምሳሌት ሀገር ” በሚል መሪ ቃል የሲዳማ ክልል ሕብረተሰብ ጤና ኢንሰቲትዩት የብልፅግና ህብረት በተለያዩ ሁነቶች በድምቀት ተከብሯል ።

የሲዳማ ክልል ሕብረተሰብ ጤና ኢንሰቲትዩት ዳይሬክተር ጀነራል ዶ/ር ዳመነ ዳባልቄ 7ተኛዉ ሀገራዊ ምርጫ ሰላማዊ ፣ ፍትሀዊ እንዲሁም የተጀመሩ ሥራዎችን ዉጤታማነት ለማስቀጥል የፖርቲዉ አባላት ቁርጠኛ መሆን እንዳለባቸዉ ተናግረዋል።

የብልፅግና ፖርቲ የሀገራችንን ህዝቦች ከተረጅነት ለማላቀቅ በመደመር መንገድ በመጓዝ ከተስፋ ብርሃን ወደ ሚጨበጥ ብርሀን ማሸጋገሩን ከዶ/ር ዳመነ ገለጻ ለመረዳት ችለናል።

የፓርቲ አባላት የሚገጥም ችግሮችን ወደ ዕድል መቀየር እንዳለባቸዉ እንዲሁም 7ተኛዉ ሀገራዊ ምርጫ በተሳካ ሁኔታ እንዲጠናቀቅ የበኩላቸዉን አስተዎፆኦ ማበርከት እንደሚገባቸዉ ከመድረኩ ተገልጿል ።

በቀረበዉ ሰነድ ላይ ሰፊ ዉይይት በማካሄድ ከአባላቱ ለተነሱ ጥያቄዎች የሚመለከታቸው አካላት ምላሽና ማብራሪያ በመስጠት የጋራ መግባባት ላይ በመድረስ ዉይይቱ ተጠናቋል።

የሲዳማ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት

ሚያዚያ 30/2018 ዓ/ም

ሀዋሳ

ለተጨማሪ መረጃዎች የሲዳማ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት:

ነፃ የስልክ መስመር፡ 7794

Web site: https://www.sphi.gov.et/

See less

Similar Posts

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *