ዘንድሮ በ2015 ዓ.ም የክረምት በጎ ተግባር ላይ
ከተሰሩ ስራዎች የሲዳማ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት በክልል ሤክተር መ/ቤቶች 1ኛ ደረጃ በመውጣት የዋንጫና የሠርተፊኬት ተሽላሚ በመሆኑ!! እንኳን ደስ አላችሁ/አለን!!!
Get the latest public health alerts and emergency updates from Sidama Public Health Institute.

ከተሰሩ ስራዎች የሲዳማ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት በክልል ሤክተር መ/ቤቶች 1ኛ ደረጃ በመውጣት የዋንጫና የሠርተፊኬት ተሽላሚ በመሆኑ!! እንኳን ደስ አላችሁ/አለን!!!

በመድረኩ ላይ ተገኝተው የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የክልሉ የብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊ ክቡር አቶ አብርሃም ማርሻሎ በንግግራቸው ከሁለት ዓመት በፍት በጤና ሴክተር ከአገልግሎት አሰጣጥ ጋር የሚያያዙ ፣ የግብዓት አቅርቦት ፣ አያያዝ እና መሰል ችግሮች እንደነበሩ ገልጸው የጤና ቢሮው አመራሮች ቆም ብለው የችግሩን ምንጮችና የመፍትሄ አቅጣጫን መቀየስ በመቻላቸው በአሁኑ ጊዜ በሴክተሩ የተሻለ ውጤት መመዝገቡን ገልጸዋል :: ኃላፊው…

የክብርት ዶ/ር ሊያ ታደሰ ሽኝት እና የጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ የአቀባበል ሥነ-ሥርዓት የክልል ጤና ቢሮ የስራ ኃላፊዎች የተጠሪ ተቋማት፣ የጤና ሚኒስቴር እንደዚሁም የፌድራል እና በአዲስ አበባ ጤና ቢሮ ስር የሚገኙ የሆስፒታሎች ኃላፊዎችና ባለሙያዎች በደማቅ ሁኔታ አከናውነዋል፡፡ በመድረኩ ሽኝት የተደረገላቸው ክብርት ዶ/ር ሊያ በጤና ሚኒስትርነት ሃገራቸውን በማገልገል ላበረከቱት ከፍተኛ አስተዋጾ እና በጤናው ዘርፍ መሪነት ላስመዘገቧቸው…

የሲዳማ ክልል ህብረተሰብ ጤና ኢንስትቲዩት አመራሮችና አጠቃላይ የፓርቲ አባላት ወቅታዊ ክልላዊና ሀገራዊ የፖለቲካ ጉዳዮች ዙሪያ በተዘጋጀ ሰነድ ላይ ውይይት አድርጓል ። የሲዳማ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ሚያዚያ 03/2017 ዓ/ም ሀዋሳ ተጨማሪ መረጃዎችን የሲዳማ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ነፃ የስልክ መስመር፡ 7794 Web site: https://sphi.gov.et/

በዕለቱ እንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር ያደረጉት የኢንስቲትዩቱ ምትክል ዋና ዳይሬክተር አቶ ኡጋሞ ሀናጋ ስሆን ኢንስቲትዩቱ ከተቋቋመባቸው ዓላማዎች መካከል በክልሉ ያለውን የጤና መረጃ በዘመናዊ መንገድ በመሰብሰብና በመተንተን ለውሳኔ ሰጪ አካላት ጥቅም ላይ እንዲውል ማድረግ መሆኑን ገልፀው ክልላዊ ጤና እና ጤና ነክ መረጃ ቅመራ፣ ትንተና እና አስተዳደር ማዕከል [Regional Data Management Center for Health(RDMS)] ተቋቁሞ ከዩኒቨርሲቲዎች፣ ከሴክተር…

በክልሉ ሰሜናዊ ዞን ሸበድኖ ወረዳ ድላ አፋራራ ቀበሌ ክልላዊ የማስጀመሪያ መረሐ ግብር ላይ ተገኝተው ክትባቱን በይፋ ያስጀመሩት የሲዳማ ክልል ጤና ቢሮ ኃላፊዋ ዶ/ር ሰላማዊት መንገሻ በበጀት አመቱ በክልሉ የመጀመሪያው ዙር የፖሊዮ ክትባት ዘመቻ የተሳካ ውጤት መመዝገቡን ተናግረዋል ፡፡ አክሎም እንደገለፁት ማህበረሰቡ አስፈላጊውን ትብብር እንዲያደርግና መከተብ ያለባቸውን ህፃናት በሙሉ እንዲያስከትቡ አሳስበዋል። በክልሉ ከአንድ ሚልየን በላይ ህጻናት…

የሲዳማ ብ/ ክ/መንግስት ጤና ቢሮ በሀገር አቀፍ ደረጃ የቲቢ በሽታን ለመግታት በተደረገው እንቅስቃሴ ከፍተኛ ውጤት በማስመዝገብ የዋንጫና የሰርተፊኬት ተሸላሚ ሆኗል:: ለዚህ ውጤት መገኘት የበኩላችሁን የተወጣችሁ የጤና ቢሮ ማኔጅመነትና ሠራተኞች እንዲሁም በተለያዩ መዋቅሮች የምትገኙ የጤናው ሴክተር አመራሮችና ባለሙያዎች እንኳን ደስ አለን /አላችሁ !! ሲዳማ ሕብረተስብ ጤና እንስቲትዩት መጋብት 13/2016 ዓ፡ም ሀዋሳ/ሲዳማ