ጤናማና አምራች አህጉር እንድትኖረን ኢትዮጵያ ከዓለም የጤና ድርጅት የአፍሪካ ቀጣና ጋር ትብብሯን አጠናክራ ትቀጥላለች – ዶ/ር መቅደስ ዳባ
**********
Get the latest public health alerts and emergency updates from Sidama Public Health Institute.

**********

__________ የPEN-Plus ብሔራዊ የአሠራር ዕቅድ ማስጀመሪያ መርሀሃ-ግብር የተካሄደ ሲሆን፤ የSTEPS የዳሰሳ ጥናት ውጤቶች ይፋ ተደርገዋል፤ ይህም ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎችን (NCDs) ለመቀነስ ቁልፍ ምዕራፍ መሆኑ ተገልጿል። በመክፈቻ ሥነ ሥርዓቱ ላይ የጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ እንደተናገሩት የሚቀጥሉት አምስት ዓመታት የመጀመሪያ ደረጃ የጤና እንክብካቤን ለማስፋፋት እና እየጨመረ የመጣውን ተላላፊ ያልሆኑ በሽዎችን ጫና ለመፍታት ወሳኝ ይሆናሉ። መንግሥት የጤና…

እንኳን ለ18ኛው የሰንደቅ አላማ ቀን በሰላም አደረሳችሁ ! የሲዳማ የሕብረተሰብ ጤና ኢንሰቲትዩት ጥቅምት 03/2018ዓ/ም ሀዋሳ ተጨማሪ መረጃዎችን የሲዳማ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ነፃ የስልክ መስመር፡ 7794 Web site: https://sphi.gov.et/

ለክልል ላበራቶሪዎች አቅም ግንባታ አገልግሎት ላይ የሚውሉት እጅግ ዘመናዊ የሆኑ የላብራቶሪ መሳሪያዎቹ ኤልኢዲ ማይክሮስኮፖችን እና ማቀዝቀዣዎችን ጨምሮ በአይነት 39 ሲሆኑ፤ ከአለም ባንክ በተገኘ ድጋፍ በአንድ ቢሊዮን ብር ወጪ የተገዙ ናቸው፡፡ ጠንካራ የጤና ስርአት ለመመስረት በዘመናዊ መሳሪያዎች የተደራጀ ላብራቶሪ ለጤናው ዘርፍ የጀርባ አጥንት መሆኑን የጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ በርክክብ መርሃ-ግቡሩ የተናገሩ ሲሆን፤ ጤና ሚኒስቴር በሽታ…

************* የማርበርግ በሽታ ስርጭትን ለመቆጣጠር የሚደረገው ጥረት ተጠናክሮ መቀጠሉን የጤና ሚኒስቴር አስታውቋል። ሚኒስቴሩ ከኢትዮጵያ የህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ጋር በመሆን የበሽታውን አሁናዊ ሁኔታ አስመልክቶ መግለጫ ሰጥተዋል። በሽታው መከሰቱ ከታወቀበት ጊዜ ጀምሮ የክትትልና የልየታ ሥራዎች እየተሰሩ መሆኑ በመግለጫው ተመላክቷል። በመሆኑም እስከ ዛሬው እለት የተለያዩ ምልክቶች ታይቶባቸው 73 ሰዎች ምርመራ ተደርጎላቸው 11 ሰዎች ቫይረሱ ተገኝቶባቸዋል። ከእነዚህም ውስጥ 6…

የሲዳማ ሕብረተሰብ ጤና ኢንሰቲትዩት ጥቅምት 27/2018 ዓ.ም ብሔራዊ የጤና መረጃ አስተዳደር ማዕከል/National Data Management Center(NDMC) እና ከክልላዊ የጤና መረጃ አስተዳደር ማዕከላት/Regional Data management Centers (RDMC) የተወጣጡ ቡድኖች በሲዳማ የጤና መረጃ አስተዳደር ማዕከል (Sidama RDMC) የተሰሩ ስራዎችን ጎብኝተዋል። በብሔራዊ የጤና መረጃ አስተዳደር ማዕከል ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች የተመራዉ አዲስ አበባንና ድሬዳዋን ጨምሮ 15 ክልላዊ የጤና መረጃ አስተዳደር…
የሲዳማ ክልል ጤና ቢሮ ሐምሌ 16/2018 ዓ.ም የሲዳማ ክልል ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ክብርት ፋንታዬ ከበደ የሚመሩት የምክር ቤቱ ቋሚ ኮሚቴዎችና አመራሮች ቡድን፣ በ2018 በጀት ዓመት በጤና ዘርፉ የተከናወኑ ሥራዎችንና የአፈጻጸም ውጤቶችን በተጨባጭ ለመገምገም የመስክ ጉብኝት ጀምረዋል። የጉብኝቱ መነሻ ደቡባዊ ሲዳማ ዞን በአለታ ወንዶ ወረዳ የሚገኘው የቤለስቶ ጤና ጣቢያ ሲሆን፣ በጤና ጣቢያው ውስጥ የተደራጁ የህክምና…