በወቅታዊ የጤና አገልግሎት ዙሪያ መረጃ ስለመስጠት
ግንቦት 07፣2017 ዓ.ም
_________
Get the latest public health alerts and emergency updates from Sidama Public Health Institute.

ግንቦት 07፣2017 ዓ.ም
_________

————————— በጉብኝቱ ወቅት ሚኒስትር ዴኤታው ከኢንስቲትዩቱ አመራሮች ጋር በነበራቸው ውይይት እንደተናገሩት ላለፉት መቶ አመታት የህብረተሰብን ጤና በማሻሻል ረገድ በፈጸመው አኩሪ ተግባር በሀገራችንም ሆነ በአለማቀፍ ደረጃ መልካም ስም ያተረፈው ይህ ኢንስቲትዩት ታሪኩን እና አገልግሎቱን የሚመጥን አሰራር እና ዉበት እንዲኖረው ለማስቻል እየተሰሩ ያሉ ስራዎች የሚያበረታቱ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡ እነዚህን ስራዎች ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ በቅርበት እንደሚከታተል የተናገሩት ዶ/ር ደረጀ…

__________ በኢትዮጵያ ጤና ሚኒስቴር እና በሩሲያ የሸማቾች መብት ጥበቃ እና የሰብአዊ ደህንነት ክትትል አገልግሎት የመግባቢያ ስምምነቱ ተፈርሟል። ፊርማው የተካሄደው ለመጀመሪያ ጊዜ የሩሲያ-አፍሪካ ለድንገተኛ የጤና አደጋዎች ፈጣን ምላሽ ሰጪ ቡድኖች ልምምድ እና አውደ-ጥናት መርሃ-ግብር ጎንዮሽ ሲሆን፤ በጤና ድንገተኛ አደጋዎች ላይ በሁለቱ አገሮች መካከል ያለውን ትብብር ለማጠናከር ያለመ ስምምነት ነው፡፡ የጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ ኢትዮጵያን ወክለው፣…

የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ከሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ እና ሌሎች አጋር አካላት ጋር በመተባበር “እናስተምር፣ እናሳውቅ፣ አሁን እንተግብር” በሚል መሪ ቃል የሚከበረውን የዘንድሮውን የዓለም ፀረ ተህዋስያን መድሐኒቶች በጀርሞች መላመድ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሳምንት ከህዳር 12-14/2017 ዓ.ም በሐዋሳ ከተማ አካሄደ፡፡ የኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር መሳይ ኃይሉ በፕሮግራሙ መክፈቻ ላይ እንደገለፁት የዓለም ፀረ ተህዋስያን የመቋቋም ግንዛቤ ማስጨበጫ ሳምንት በዓለም አቀፍ…

የከፍተኛ አመራር እና የባለድርሻ አካላት ወቅታዊ የወባ ስርጭት ጫናን በዘላቂነት የመግታት አድቮኬሲ መድረክ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሚዛን አማን ከተማ ተካሂዷል። የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴዔታ ዶክተር ደረጀ ዱጉማ ባልተጠበቀ ሁኔታ እየጨመረ የመጣውን የወባ በሽታ ስርጭት በህብረተሰቡ ላይ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ቀውሶችን አስከትሏል ብለዋል። በሀገራችን 75 ከመቶ የሚሆነው አካባቢ ለወባ በሽታ ስርጭት አመቺ መሆኑን የጠቆሙት ሚኒስትር ዴዔታ፣…

የሲዳማ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ለይርጋለም ሆስፒታል ህክምና ኮሌጅ ላቦራቶሪ ባለሙያዎች የማይክሮባዮሎጂ ምርመራ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ የአቅም ግንባታ ስልጠና ለአምስት ተከታታይ ቀናት በህብረተሰብ ጤና ላቦራቶሪ ከተሰጠ በኃላ ተጠናቋል። የሲዳማ ሕብረተሰብ አና ኢንስቲትዩት ግንቦት 4/2017ዓ/ም ሐዋሳ ተጨማሪ መረጃዎች ============= የሲዳማ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ነፃ የስልክ መስመር፡ 7794 Web site: https://sphi.gov.et/
