አሳዛኝ ዜና
እህታችን ስምረት ባደረባት ህመም በህክምና ስትረዳ ቆይታ ትናንት ምሽት አርፋለች ። ስለሆነም የአስከሬን አቀባበል ለማድረግ ዛሬ 8:00 ላይ ጥቁር ዉሀ እንገናኝ ።
ፈጣሪ ለቤተሰብ እንድሁም ወዳጅ ዘመድ መፅናናትን ይስጥ።




Get the latest public health alerts and emergency updates from Sidama Public Health Institute.






የሲዳማ ክልል ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ዳይሬክተር ጄነራል ዶ/ር ዳመነ ደባልቄ ከአዲስ አበባ ለመጡ ልዑካን ቡድን አባላት መልዕክት ከአስተላለፉ በኃላ በአጠቃላይ በኢንስቲትዩቱ ደረጃ የተሰሩ ሥራዎች ላይ ገለጻ ተደርጓል። በመቀጠልም እንግዶቹ በተቋሙ ከሚገኙ ዳይሬክተሮች አማካኝነት የሥራ ምልከታና ልምድ ልውውጥ አድርገዋል። በተጨማሪም የልዑካን ቡድን አባላት፤ የሕብረተሰብ ጤና ድንገተኛ አደጋዎች ቅኝትና ምላሽ፣ የጤና መረጃ አስተዳደር ቅመራና ትንተና፣ የሕብረተሰብ ጤና…

የልምድ ልውውጥ ቡድን አባላትን እንኳን በደህና መጣችሁ በማለት መግቢያ ንግግር በማድረግ ያስጀመሩት የሲዳማ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ዳመነ ደባልቄ ሲሆኑ በክልሉ እየተተገበረ ያለውን የመረጃ አያያዝ /ዳታ ማናጅመንት ሲስተም ፣ ነፃ የስልክ ጥሪ ማእከል (free call center) ፣ የሕብረተሰብ ጤና ድንገተኛ አደጋዎች ቁጥጥር ፣ የክልሉ ላቦርቶሪ እና ጤና ምርምርና ተክኖሎጂ ሽግግር ስራዎች ላይ ገለጻ…

።።።።።።።።።።።።።።። የሲዳማ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የላቦራቶሪ አለም አቀፍ ስታንዳርድ (ISO 15189:2012)ን ተከትሎ እየሰራ መሆኑ ተረጋግጠው በEID,HIV viral load,Genexpert እና TB culture ላይ ከኢትዮጵያ አክሬድተሽን አገልግሎት የአክሬድተሽን ሰርተፍኬት ተበርክቶልናል። የሲዳማ ሕብረተስብ ጤና ኢንስቲትዩት ለተገኘው እውቅና የተሰማውን ደስታ ይገልጻል !! የሲዳማ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ነሐሴ 15/2017 ዓ/ም ሀዋሳ ተጨማሪ መረጃዎች የሲዳማ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ነፃ የስልክ መስመር፡…

ሲዳማ ክልል “የጤናው ዘርፍ አርበኝነት ለሀገር እድገት!” በሚል መሪ ቃል የተዘጋጀ ክልላዊ የጤና ባለሙያዎች የውይይት መድረክ ዛሬ በሀዋሳ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል። የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደስታ ሌዳሞ በመድረኩ ተገኝተው እንደገለፁት ሲዳማ ክልል ከሆነ ጀምሮ ህብረተሰቡ ያነሳቸውን የልማት ጥያቄዎች መነሻ በማድረግ በመሠረተ-ልማት፣ በኢኮኖሚ፣ በማህበረሰብ አቅም ግንባታ እንዲሁም የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን ለመመለስ በተደረገው ጥረት ባለፉት አምስት…

——————————– የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የሀገሪቱን የጤና ደህንነትና የወረርሽኝ መከላከል አቅም በምርምር ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር ያለመ ስትራቴጂካዊ የምክክርና የግብዓት ርክክብ መድረክ ከክልል አቻ ተቋማት ጋር አካሂዷል። በመድረኩ ላይ የኢንስቲትዩቱ ምክትል ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ጌታቸዉ ቶሌራ እና የተላለፊ በሽታዎች ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ዶ/ር ገመቹ ታዳሰ የጀኖሚክስ እድገትን አስመልክቶ ሰፊ ማብራርያ አድርገዋል፡፡ በመድረኩ ከኦሮሚያ፣ ከአማራ፣ ከሲዳማ እና…

የሲዳማ ሕብረተሰብ ጤና ኢንሰቲትዩት ፤ ሀምሌ 22/2016 ማዕከላዊ ሲዳማ ዞን ወንሾ ወረዳ ግሽሬ፤ጉዱሞና ሆሞ ተብሎ የሚጠራ አከባቢ ትናንት በጣለው ከፍተኛ ዝናብ ምክንያት መሬት በመንሸራተቱ የ11 ሰዎች ህይወት ሲያልፍ ስድስት ሰዎች ደግሞ ጉዳት ደርሶባቸዋል። የክልሉ መንግሥት ከዞን አስተዳደር ጋር በመሆን አደጋ ከደረሰ ስዓት አንስቶ ለዜጎች ተጨማሪ አደጋ ኢንዳያደርስ የማድረጉ ስራና ተጎጂዎች ህክምና እንዲያገኙ አድረጓል። የክልሉ መንግሥት…