ጤናማና አምራች አህጉር እንድትኖረን ኢትዮጵያ ከዓለም የጤና ድርጅት የአፍሪካ ቀጣና ጋር ትብብሯን አጠናክራ ትቀጥላለች – ዶ/ር መቅደስ ዳባ
**********
Get the latest public health alerts and emergency updates from Sidama Public Health Institute.

**********

____________ የጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ በወቅታዊ የጤና ጉዳይ ላይ ለጋዜጠኞች መግለጫ ሰጥተዋል። በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጅንካ ከተማ የማርበርግ ቫይረስ በሽታ መከሰቱ በላቦራቶሪ መረጋገጡ መገለጹን ያስታወሱት ሚኒስትሯ እስካሁንም ድረስ 17 የተጠረጠሩ ሰዎች ምርመራ ተደርጎላቸዋል፣ ከዚህም 3ቱ ህይወታቸው በቫይረሱ ያለፈ መሆኑን በኢትዮጵያ ህብረተሰብ ኢንስቲትዩት ሪፈረንስ ላቦራቶሪ መረጋገጡ፣ በተጨማሪም በምርመራ የተረጋገጠ ባይሆንም 3 ምልክቶች የታየባቸው ሰዎችም ህይወት…

የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ከቶኒ ብሌየር ኢንስቲትዩት ፎር ግሎባል ቼንጅ (Tony Blair Institute for Global Change [TBI]) ጋር በመተባበር የሕብረተሰብ ጤና ስራ አመራር የአቅም ግንባታ ፕሮግራም አካል ከሆነው አንዱ የዴሊቨሪ ሜካኒዝምስ ስልጠና ለኢንስቲትዩቱ አመራር አባላት ከሰኔ 14-15/2016 ዓ.ም ሰጠ፡፡ የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር መሳይ ኃይሉ:- ይህ ስልጠና ኢንስቲትዩቱ የሚያከናዉናቸው ዘርፈ ብዙ ስራዎችን በተቀናጀ መልኩ በይበልጥ…

በሲዳማ ሕብረተሰብ ጤና ኢንሰቲትዩት የ2017 በጀት ዓመት የላቦራቶሪ አገልገሎት ሥራ አፈጻጸም ግምገማ እና የጥራት ማሻሻያ ፕሮግራሞች ማለትም የዓለም አቀፍ መስፈርትን ለማሟላት ደረጃ በደረጃ በማሻሻል የኮከብ ዕውቅና ( ኮከብ1-4)፤በላቦራቶሪ ምርመራ አገልግሎት በዓለም አቀፍ የላቦራቶሪ ጥራት ማረጋገጫ መስፈርት (ISO-15189) መሰረት እውቅና እና በአዲስ ኮከብ ላገኙና ላሰቀጠሉ የጤና ተቋማት እውቅና ተሰጥቷል ። በመድረኩ ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የዕለቱ…

የዛሬ አንድ አሜት ገደማ Resolve to Save lives የሚባል መንግስታዊ ያልሆኔ ድርጅት ከሲዳማ ክልል ጤና ቢሮ እና ከህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ጋር በመተባበር በ 8 ወረዳ እና በአንድ ከተማ አስተዳደር ውስጥ በሚገኙ በ23 ጤና አጠባበቅ ጣቢያዎች ድንገተኛ የህብረተሰብ ጤና አደጋዎች ከተከሰቱ በብቃት ለመመከት እንዲሁም በዘላቅነት መደበኛ የጤና አገልግሎቶች ሳይስተጎጉል ለማስቀጠል ዝግጁ የሆኔ የመጀመሪያ ጤና ክብካቤ አሃድ…

• እጅዎን በውሃና በሳሙና ይታጠቡ ወይም በሳኒታይዘር ያጽዱ • ማስክ ያድርጉ • በቂ የአየር ዝውውር እንዲኖር መስኮቶችን ይክፈቱ • የሕመም ምልክት ከተከሰተ ወደ ጤና ተቋም ይሂዱ • ፈሳሽ ይውሰዱ፤ በቂ ዕረፍትም ያድርጉ የዛሬ ጥንቃቄዎ ለነገ ጤናዎ!! ለተጨማሪ መረጃ 8335 ነፃ የስልክ መስመር ይደውሉ የኢትዮጵያ የሕብረሰተብ ጤና ኢንስትቲዩት

፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨ የማርበርግ ቫይረስ (Marburg virus) በማንኛውም ንክኪ መተላለፍ የሚችል እጅግ በጣም አደገኛ በሽታ በመሆኑ የገጻችን ተከታዮች ጥንቃቄ እንዲያደርጉ እንመክራለን። ከማንኛውም መነካካት (መጨባበጥ) እንዲቆጠቡ በመደበኛነት የእጅ ሳኒታይዘር እንዲጠቀሙ ማንኛውንም ነገር ከነኩ በኋላ እጆችን በሚገባ እንዲያጸዱ እንመክራለን! ሰው በሚበዛባቸው እና ከፍተኛ መነካካት በሚያስከትሉ አካባቢዎች ከፍተኛ ጥንቃቄ ማድረግ ይገባል። #MarburgVirus የሲዳማ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲዩት ህዳር 18/2017 ዓ.ም ሐዋሳ…