የኢትዮጵያ ሕብረተሰብ ጤና ኢንሰቲትዩት የተመሠረተበትን 100ኛ ዓመት ( Centenary) ክብረ በዓል አስመልክቶ የሲዳማ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላለፈ ።

የሲዳማ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት

ሐምሌ 7/2018 ዓ.ም

የሲዳማ ሕብረተሰብ ጤና ኢንሰቲትዩት አመራሮችና አጠቃላይ ሠራተኞች ፦ የኢትዮጵያን የጤና አገልግሎት ለማሻሻል ጉልህ አሰተዋጽኦ ላስመዘገበው ለኢትዮጵያ ሕብረተሰብ ጤና ኢንሰቲትዩት (EPHI) ለመቶኛ ዓመት የምሥረታ ክብረ በዓል እንኳን አደረሳችሁ / እንኳን ደስ አላችሁ!!

የኢትዮጵያ ሕብረተሰብ ጤና ኢንሰቲትዩት ባለፉት 100 ዓመታት የተጓዘበት ረጅም ምዕራፍ ፤ የሀገራችንን ሕብረተሰብ ከወርሸኝ ለመጠበቅ፣ የህብረተሰቡን የጤና ችግር በምርምር በመፍታት፣ ወረርሽኞች ሲከሰቱ የወረርሽኞችን መንስኤ በላቀ የላቦራቶሪ ምርመራ በማረጋገጥ ያበረከተው አሰተዋጽኦ ታሪካዊ ነው።

ይህ የመቶ ዓመት ታሪካዊው ጉዞ የተቋሙን ተልዕኮ ክንውን ፣ የህዝባችንን ሁለንተናዊ የጤና አገልግሎት ተጠቃሚነትና ብሔራዊ የጤና ደህንነትን ማረጋገጥ እና ዘመናዊ ቴክኒዎሎጂዎችን ተግባራዊ ማድረግ ዋና ዋናዎቹ የኢንስቲትዩቱ ስኬት ናቸው ።

ስለሆነም መላው የኢትዮጵያ ሕብረተሰብ ጤና ኢንሰቲትዩት አመራሮች ፣ የሕብረተሰብ ጤና ድንገተኛ አደጋዎች ቁጥጥር ዊንግ ባለሙያዎች ፣ ተመራማሪዎች ፣የላቦራቶሪ ባለሙያዎች ፣የብሔራዊ የጤና መረጃ አስተዳደር ባለሙያዎችና የድጋፍ ሠራተኞች በሙሉ:-እንኳን ለ100ኛ ዓመት ክብረ-በዓል አደረሳችሁ !

ዶ/ር ዳመነ ደባልቄ

የሲዳማ ሕብረተሰብ ጤና ኢንሰቲትዩት ዳይሬክተር ጀነራል

የሲዳማ ክልል የህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት

ሀምሌ 7/2018 ዓ/ም

ሀዋሳ

ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች

👇👇👇👇 ይመልከቱ

ነፃ የስልክ መስመር፡ 7794

Web site: sphi.gov.et/emergency

Facebook: https://web.facebook.com/profile.php?id=100083576610173

Telegram: https://t.me/c/1865772308/1

Email:- admin@sphi.gov.et

See less

Similar Posts

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *