የሀገራችንን የሳይንስና የጤና ሉዓላዊነት በተሟላ ሁኔታ ለማረጋገጥ በቁርጠኝነት እንሰራለን፦ የኢትዮጵያ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር መሳይ ኃይሉ

​የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር መሳይ ኃይሉ ባደረጉት ታሪካዊና ጠንካራ ንግግር፤ ተቋሙ ላለፉት መቶ ዓመታት በሳይንስ፣ በምርምርና በፈጠራ የታገዘና በመላው ኢትዮጵያውያን ዘመናዊ የሕብረተሰብ ጤና እንክብካቤን ያስጀመረ ብቸኛና አንጋፋ የሕዝብ አገልጋይ መሆኑን ገልጸው፣ ይህ ዕለት የጤና ሥርዓቱን ለመገንባትና የሕዝብን ደህንነት ለመጠበቅ ያላሰለሰ ጥረት ያደረጉ ውድ ባለወለታዎችን በታላቅ አክብሮት የምናመሰግንበትና ለቀጣዩ ትውልድ የተሻለ የጤና ሥርዓት ለመገንባት ቃል የምንገባበት ልዩ የታሪክ ምዕራፍ መሆኑን አስገንዝበዋል። ዋና ዳይሬክተሩ አክለውም፣ ባለፉት መቶ ዓመታት የተመዘገቡ ስኬታማ የሥራ መሠረቶችን ይዞ በመነሳት፣ በቀጣዩ መቶ ዓመታት በተሻለ ዝግጁነትና አቅም የሚሠራ ተቋም በመገንባት የሀገራችንን የሳይንስና የጤና ሉዓላዊነት በተሟላ ሁኔታ ለማረጋገጥ በቁርጠኝነትና በ”ይቻላል” መንፈስ እንደሚሠራ በፅናት አረጋግጠዋል(EPHI)::

See less

Similar Posts

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *