
Similar Posts

የሲዳማ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ለክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለብርሀነ መስቀሉ በሰላም አደረሳችሁ እያለ በዓሉ የሰላም እና የጤና እንዲሆንላችሁ ምኞቱን ይገልጻል፡፡
Byadminየሲዳማ የሕብረተሰብ ጤና ኢንሰቲትዩት መሰከረም 16/2018ዓ/ም ሀዋሳ ተጨማሪ መረጃዎችን የሲዳማ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ነፃ የስልክ መስመር፡ 7794 Web site: https://sphi.gov.et/

የሲዳማ ክልል ሁሉም ኢትዮጵያውያን በክብርና በአንድነት የሚኖሩበት የህብራዊነት መገለጫ ነው:- ም/ርዕሰ መስተዳድርና የት/ት ቢሮ ኃላፊ አቶ በየነ ባራሳ
Byadminየሲዳማ ክልል ሁሉም ኢትዮጵያውያን በክብርና በአንድነት የሚኖሩበት የህብራዊነት መገለጫ ነው ሲሉ የሲዳማ ክልል ም/ርዕሰ መስተዳድርና የት/ት ቢሮ ኃላፊ አቶ በየነ ባራሳ ገለጹ። በሲዳማ ክልል የጳጉሜ 2 የህብር ቀን ”ብዝኃነት የኢትዮጵያ ጌጥ” በሚል መሪ ቃል በተለያዩ መርሐግብሮች ተከብሯል። ዕለቱን አስመልክቶ መልዕክት ያስተላለፉት አቶ በየነ ባራሳ አንደገለጹት እናት ሀገራችን ኢትዮጵያ በብዝሀ ማንነቶች የጠነከረች የሁላችንም ቤት ናት ብለዋል፤…

ሳምንታዊ የህብረተሰብ ጤና አደጋዎች ክስተት አስተዳደር ስርዓት (Regional Incident Management System) በክልሉ የህብረተሰብ ጤና አደጋዎች ቅኝትና ምላሽ ማስተባበሪያ ማዕከል (PHEOC) ሥራዎች በዛሬዉ ዕለት ባለድርሻ አካላት በተገኙበት ተገምግሟል፡፡
Byadminየሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ጤና ቢሮ፣ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩትና ሌሎች ባለድርሻ አካላት በተገኙበት በክልሉ አንዳንድ አከባቢ የተከሰቱ የኮሌራ ወረርሽኝ እና የወባ በሽታ ስርጭት ያለበት ደረጃ ተገምግሟል፡፡ መድረኩን በይፋ ያስጀመሩት የክልሉ ጤና ቢሮ ኃላፊዋ ዶ/ር ሰላማዊት መንገሻ ሲሆኑ ከክረምት ጋር ተያይዞ አንዳንድ ወረዳዎች የተከሰቱ የኮሌራ ወረርሽኝ እና የወባ በሽታ ስርጭት ከሚጠበቀዉ በላይ መሆኑ አሳሳቢ የህብረተሰብ ጤና…

የጤና ሚኒስቴር ከሲዳማ ክልል ጤና ቢሮ ጋር በመተባበር ለጤና ኤክስቴንሽኖችና ለጤና ባለሙያዎች በማርበርግ ቫይረስ በሽታ ላይ ስልጠና እየሰጠ ነው።
Byadminየሲዳማ ክልል ጤና ቢሮ ህዳር 20/2018 ዓ.ም የጤና ሚኒስቴር ከሲዳማ ክልል ጤና ቢሮ ጋር በመተባበር በየደረጃው ለሚገኙ የጤና ባለሙያዎችና የጤና ኤክስቴንሽን ባለሙያዎች በማርበርግ ቫይረስ በሽታ ላይ ስልጠና እየሰጠ መሆኑ ታውቋል። የሲዳማ ክልል ጤና ቢሮ ምክትልና የጤና ፕሮግራሞች ዘርፍ ሀላፊ አቶ በላይነህ በቀለ በመልዕክታቸው የማርበርግ ቫይረስ በሽታ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጂንካ ከተማ መከሰቱ ከታወቀበትና በነበረው ቀጥተኛ…

ወረርሽኞችን ለመቆጣጠር በሚኖሩት ምላሽ መስጠት ስራዎች ውስጥ ለተቋማት ቅንጅታዊ ስራን ለማጠናከር እድል እንደሚፈጥር ተገለፀ።
Byadminየአርማወር ሐንሰን የምርምር ኢንስቲትዩት አመራሮችና ተመራማሪዎችን ያቀፈ ልዑክ፣ በማርበርግ ቫይረስ ወረርሽኝ መከላከልና በክትባት ምርምር ዙሪያ ያለውን አገራዊ ምላሽ ለመገምገም በሲዳማ ክልል ሀዋሳ ከተማ የመስክ ጉብኝት አከናወኑ። ይህ ጉብኝት የጤና ሚኒስቴር የተሰጠውን አገራዊ የምላሽ አሰጣጥ ተልዕኮ መነሻ ያደረገ ሲሆን፣ በሲዳማ ክልል ሪጅናል ላብራቶሪ እና በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ሆስፒታል ውስጥ ያለውን የማርበርግ ክትባት መስጫ ማዕከል ወረርሽኙን ለመግታት…

