ኢንስቲትዩቱ በላብራቶሪ አቅም ግንባታ እና ጥራት ማስጠበቅ

በጤናው ዘርፍ የላብራቶሪ አቅም ግንባታ እና ጥራት ማስጠበቅ (Laboratory Capacity Building and Quality Assurance) የሕክምና አገልግሎት ጥራት፣ የታካሚዎች ደህንነት እና የሕዝብ ጤና ጥበቃ ዋና መሠረት ነው። የላብራቶሪ ምርመራ ውጤት ሐኪሞች ለሚሰጡት ውሳኔ ከ70 በመቶ በላይ ድርሻ እንዳለውም ይገመታል። ለዛም ነው ላብራቶሪ የህክምናው ዘርፍ የጀርባ አጥንት ነው የሚባለው፡፡ የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩትም የላብራቶሪ አቅምን ለመገንባትና ጥራትንም ለማረጋገጥ በርካታ ስራዎችን እያከናወነ ይገኛል፡፡

በኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት በላብራቶሪ አቅም ግንባታ ዳይሬክቶሬት የላብራቶ ጥናት ትግበራ ዲቪዢን ሃላፊ አቶ አዋድ መሃመድ እንደሚናገሩት የኢትዮጵያ የህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የሪፈራል እና ሪፈረንስ ላብራቶሪ ዳይሬክቶሬት በየጊዜው አዳዲስ ምርመራዎችን እያስተዋወቀ ይገኛል፡፡ በዚህ አመትም በጣም ብዙ የላብራቶሪ ምርመራዎችን ማስተዋወቅ ተችሏል። ብዙ ገንዘብና ግዜ የሚወስዱ በውጪ ሀገር የሚሰሩ የላብራቶሪ ምርመራዎችን በዝቅተኛ ዋጋ ለህብረተሰቡ ማቅረብ ችሏል፡፡ ለህብረተሰብ ጤና አስተዳደር የሚያስፈልጉ ምርመራዎችንም በየጊዜው እያስተዋወቀ ይገኛል፡፡

እነዚህ የሪፈራል እና ሪፈረንስ ላብራቶሪዎች ከጥራት አኳያ ሲታዩ በISO 15189 የጥራት እውቅና የተሰጣቸው ናቸው፡፡ ISO 15189 ደግሞ ለሜዲካል ላብራቶሪ የተዘጋጀ አለም አቀፍ የጥራት ደረጃ ነው። በኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ያሉት የሪፈራል ላብራቶሪዎች ሁሉም ይህንን የጥራት መስፈርት አሟልተዋል፡፡ ይህም ላብራቶሪዎቹ በየትኛውም አለም ተቀባይነት እንዲኖራቸው ያደርጋል፡፡

አሁን ላይ ደግሞ አንቲ-ዶፒንግ (Anti-Doping) ምርመራ በሀገር አቀፍ ደረጃ ማድረግ የሚያስችል አቅም ተፈጥሯል:: ይህም በቅርቡ የሚጀመር ይሆናል፡፡ ብዙ ጊዜ አትሌቶች ይህን ምርመራ የሚያደርጉት በውጪ ሀገር ነበር፡፡ አሁን ላይ ግን ይህን ምርመራ በሀገር ውስጥ ማድረግ ተችሏል፡፡ ስለዚህ ወደፊት ለኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን ለጎረቤት ሀገራትም ጭምር ምርመራ ለማድረግ የሚያስችል አቅም ተገንብቷል፡፡

ሌላው የላብራቶሪ አቅም ግንባታ ስራ የሚሰራው አጠቃላይ የላብራቶሪ አገልግሎት ጥራታቸውን የጠበቁ እንዲሆኑ ድጋፍ ማድረግ ሲሆን እንደ ኢትዮጵያ የላብራቶሪ አገልግሎት ጥራትን በሶስት መንገዶች እንዲጠበቅ ይደረጋል፡፡ አንደኛው ለጤና ተቋማት የተዘጋጁ የጥራት መጠበቂያ ስረአትን ተግባራዊ በማድረግ ነው፡፡ ሁለተኛ ደግሞ በዋነኝነት ለሆስፒታል ላብራቶሪ የተዘጋጀውን የጥራት ማስጠበቂያ ፕሮግራም ተግባራዊ እንዲደርጉ በማድረግ ሲሆን ሶተኛውና የመጨረሻው የክልል ሪፈራል ላብራቶሪዎች እና ሀገር አቀፍ ሪፈራል ላራቶሪዎች የአለም አቀፍ ስታንዳርድ ማለትም የ15185 (15189) ተግባራዊ እንዲያደርጉ የሚያወጡት የምርመራ ውጤት ታማኝነት እንዲኖረው የሚያረጋግጥ ስራ የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት በዋናነት ይሰራል፡፡

ስለዚህ አጠቃላይ የክልል፣ ሆስፒታል፣ የፌደራል ሆስፒታሎች ላብራቶሪዎች ላይ የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩ የላብራቶሪ ጥራት ተግባራዊ እንዲሆን ድጋፍ ያደርጋል። በተዋረድ ደግሞ የክልል ሪፈራል ላብራቶሪዎች የራሳቸውን እና በስራቸው ያሉ ፋሲሊቲዎችንድጋፍ ያደርጋሉ፡፡ ስለዚህ ኢንስቲትዩቱ የክልል ሪፈራል ላብራቶሪዎችን ወይም የህዝብ ጤና ኢንስቲትዩቶችን ይደግፋል፡፡

ስለዚህ እነሱ ደግሞ በተዋረድ ወደ ታች ላለው ላብራቶሪ ተመሳሳይ ድጋፍ ያደርጋሉ፡፡ ኢንስቲትዩቱም አቅም በየቦታው እየገነባ ነው ያለው፡፡ የክልል ሪፈራል ላብራቶሪዎች ደግሞ በተዋረድ የድጋፍ ስራቸውን ይሰራሉ፡፡ ከዚህ አንፃር ጥራትን ለማስጠበቅ የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ይሰራል፡፡

ስለዚህ እንደ ሀገር በኢትዮጵያ የISO 15189 የጥራት ደረጃን ያሟሉ ወደ 75 የሚሆኑ ላብራቶሪዎች አለም አቀፍ እውቅና አግኝተዋል። ነገር ግን አሁን ካሉት 4,500 በላይ ላብራቶሪዎች ቁጥር አንፃር ሲታይ ገና ነው፡፡ ስለዚህ እዚህ ላይ ወደፊት ብዙ ስራ መሰራት እንዳለበት የሚጠቁም ነው። እንዲያም ሆኖ ኢትዮጵያ የላብራቶሪ ጥራት ቁጥጥር ስረአትን ተግባራዊ በማድረግ እና የISOን እውቅና በማምጣት በአፍሪካ አራተኛ ደረጃ ይዛለች፡፡

ይህም እንደ አፍሪካ ኢትዮጵያ በጣም ጥሩ ደረጃ ላይ እንደምተገኝ ያሳያል፡፡ ነገር ግን ደግሞ ባጠቃላይ ሲታይ የጥራት ቁጥጥር ስረአት ወይም ደግሞ የጥራት ደረጃ አሁንም ገና የሚቀረው መሆኑን ያሳያል፡፡ ስለዚህ የኢትዮጵያ ደረጃ በአፍሪካ ጥሩ ቢሆንም እንደ ሀገር ካሉት የላብራቶሪዎች ብዛት አንጻር አሁንም በጣም ብዙ መስራት ይጠበቃል፡፡

አቶ አዋድ እንደሚሉት ሌላው ከላብራቶሪ ጥራት ጋር ተያይዞ ያለው ፕሮግራም የውጪ ጥራት ምዘና (External Quality Assessment) ሲሆን ይህም ላብራቶሪዎች የሚሰሯቸው ስራዎች ታአማኒነታቸውን የሚከታተል ስረአት ነው፡፡ በዚህም ውስጥ ሶስት አይነት ስረአቶች አሉ፡፡ አንደኛው እንዲሞከሩና በትክክል ይሰራሉ ወይስ አይሰሩም የሚለውን ለማየትና ጥራታቸውን ለማረጋገጥ እንደ ሀገር ከውጭ ኮንትራት ተደርጎ የሚመጣ የውጪ ጥራት ምዘና ነው፡፡

ሁለተኛው ደግሞ በሀገር አቀፍ ደረጃ የሚሰራ ፒቲ ፓናል አለ። ስለዚህ እነዚህን በመጠቀም የላብራቶሪ አቅማቸውን ከጥራት አንጻር መመዘኛ ስረአት ሲሆን ላብራቶሪዎቹ በትክክል አገልግሎት እየሰጡ መሆኑንና አለመሆኑን ያረጋግጣል፡፡ ከዚህ ውስጥ አንደኛው ድጋሚ ማረጋገጥ ወይም (Re-checking) ስረአት ሲሆን ይህም ላብራቶሪዎች የሰሩትን ናሙና ወይም ስላይድ በትክክል ነበረ ወይ የሰሩት የሚለውን ነገር በድጋሚ የማረጋገጥ ስራ የሚሰራበት ነው፡፡ ።

ሶስተኛው ደግሞ ኦንሳይት ኢቫሉዌሽን (On-site evaluation) ነው። ላብራቶዎች እየሰጡት ያለው አገልግሎት ከጥራት አንፃር ልክ ነበረ ወይ የሚለውን አጠቃላይ ስረአቱን ክትትል የሚደረግበት ነው፡፡ ስለዚህ እነዚህን ሶስት መንገዶች በመከተል ላብራቶሪዎች የሚሰጡት አገልግሎት ጥራቱን የጠበቀ የተጠበቀ መሆኑን፣ እምነት የሚጣልበት መሆኑን እና በትክክለኛው ጊዜ መውጣት መቻሉን ለማረጋገጥ የኢትጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ከክልል ሪፈራል ላብራቶሪዎች ጋር በመሆን ድጋፍ ያደርጋል፡፡ ኢንስቲትዩቱ በተዋረድ በአብዛኛው የክልል ሪፈራል ላብራቶሪችንና የህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩቶችን አቅም ከማሳደግ አንጻር አጠቃላይ ድጋፍ ያደርጋል፡፡

ከዚህ ጋር ተያይዞ አንደኛው በኢንስቲትዩቱ እየተሰራ ያለ ስራ አለ። በናሽናል ደረጃ የኢኪውኤ (EQA) ሳምፕል ለማምረት የሚያስችል እቅድ ተይዟል፡፡ የህንፃ ግንባታው ተከናውኗል፡፡ ይህም ወደፊት በሀገር አቀፍ ደረጃ ብዙ ተሳታፊዎችን በዚህ ስረአት ውስጥ ማስገባት ያስችላል፡፡ በተጨማሪ ደግሞ ከዋጋ አንጻርም ሲታይ በጣም ብዙ የሚታደግ ስራ ነው።

See less

Similar Posts

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *